Sunday, October 15, 2017

በሱማሌ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ በደረሰ የሽብር ጥቃት 85 ሰዎች ሞቱ፡፡

በሱማሌ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ በደረሰ የሽብር ጥቃት 85 ሰዎች ሞቱ፡፡

 ባህር ዳር፡ ጥቅምት 5/2010 ዓ/ም (አብመድ)ሞቃዲሾ ላይ በደረሰው አደጋ ሀላፊነቱን የወሰደ ባይኖርም ሀገሪቱ በተደጋጋሚ የአልቃኢዳ እና አልሸባብ ኢላማ ሆና ቆይታለች፡፡ በተፈጸመው የሽብር ጥቃት ሞቃዲሾ ሀዘን ላይ ነች፡፡ሶማሊያ በፕሬዝዳንት ሙሀመድ ፋርማጆ አማካኝነት 3 የሀዘን ቀናትን አውጃለች፡፡ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ተነግሯል፡፡ ምንጭ፡-ቢቢሲ

ደብረ ማርቆስ ከተማ ከኦሮምያ እንቦጭን ለማስወገድ ለመጡት ወጣቶች ውብ አቀባበል አድርጋለች፡፡

ደብረ ማርቆስ ከተማ ከኦሮምያ እንቦጭን ለማስወገድ ለመጡት ወጣቶች ውብ አቀባበል አድርጋለች፡፡

 ዛሬ ቀኑ ጥቅምት 2/2010 ዓ/ም ነው፡፡ጥቅምት 2 ደግሞ ኢትዮጵያውን አርበኞች ወራሪውን የጣልያን ፋሺስት በመጣበት እንዲመለስ ‹‹ወረኢሉ ከተህ ላግኝህ›› በተባለው መሠረት የጉዞ መነሻቸው ዕለት ነው፡፡ ዛሬም በጣና ህልውና ላይ የመጣውን ወራሪ ቅጠል ለማስወገድ ከኦሮምያ ክልል ከተለያዩ አካባቢዎች የተሰባሰቡ ወጣቶች ወደ አማራ ክልል በመጓዝ ላይ ናቸው፡፡በአንድነት በመተሳሰብና በመፈቃቀር የተጀመረው ጉዞ ጣና ላይ …ጣናን ባለበት ለማጽናት የሁሉንም ይሁንታ በሚፈልገው ጣና ተገኝተው የድርሻቸውን ይወጣሉ፡፡ወጣቶቹ በአማራ ክልል በሚደርሱበት ቦታ ሁሉ አቀባበል ውብ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡፡፡ የአባይ ገባር የሆነው ጣና ጉዳቱ ከጨመረ መጨረሻው በህዳሴው ግድብ ላይ ሌላ የአደጋ ስጋት ይሆናል፡፡ጣናን መታደግ አባይን መታደግ ነው፡፡ ሁሌም ለስራ ዝግጁ የሆነው የወጣት ጉልበት በእምቦጭ አረም ላይ ዘምቶ ውጤት እንደሚያስመዘግብ ጥርጥር የለውም ፡፡

Saturday, September 9, 2017

የቡርማ ሙስሊሞች ጉዳይ


ከጊዜህ ላይ 90 ሴኮንድ ወስደህ ስለ ቡርማ ሙስሊሞችን ችግር ብታውቅ ምን ይመስልሃል?
ታሪኩ ባጭሩ ይህን ይመስላል!
3,000,000 ሙስሊሞች የሚኖሩባት አራካን የተሰኘች አንዲት ሃገር ነበረች። ከዚች ሃገር ጎረቤት በሆነችው ቡርማ የአራካን ሙስሊሞች በሚያደርጉት ዳዕዋ ምክንያት እስልምና አየተስፋፋ ሄደ። ቡርማ ውስጥ አብዛሃኛው ማህበረሰብ የቡድሃ እምነት ተከታይ ነው። በ1784 /ማለትም ከዛሬ 230 አመታት በፊት/የቡርማ ቡድሂስቶች በአራካን ሙስሊሞች ላይ ባሳደሩት ቂም ምክንያት ወረራ በመፈፀም ብዙ ሙስሊሞችን ገደሉ። አራካንንም ወደ ቡርማ በማስገባት መጠሪያዋን ሚንማር የሚል ስም አደረጉ። ሙስሊሞች አነስተኛውን ቁጥር የሚይዙ ሲሆን ብዛታቸው ከ 3 ― 4 ሚሊዮን ይደርሳል።


በአንፃሩ ደግሞ ቡድሂስቶች 50,000,000 ይሆናሉ።
ሙስሊሞች የራሳቸውን መንደር በማበጀት የንግድ ልውውጦች እና የራሳቸውን ማህበራዊ ህይወት መምራት ጀመሩ። በዚቹ መንደር ውስጥ የተለያዩ ማህበራት ያሉ ሲሆን መሳጂዶችንና ዱኣቶችን ይደጉማሉ።

አሁንም የቡርማ ቡድሂስቶች ወደ ሙስሊሞች መንደር በመዝመት ከሃገር ለማስወጣት እንቅስቃሴ ጀመሩ። ብዙም ሳይቆይ አሰቃቂ የሆነ ግድያ (እርድ) ፈፀሙ። ይህም የሆነው በሙስሊሞች አካባቢ በመዘዋወር ሰዎችን የሚያስተምሩ ፣ ኒካህ የሚያስሩ ፣ ቁርኣን የሚያስቀሩ ወደ አስር የሚጠጉ ሃፊዞችንና ዳኢዎችን በመያዝ ብርቱ የሆነ ድብደባ ፈፀሙባቸው።

ይህም አልበቃ ብሏቸው ሰውነታቸውን በሳንጃ ተጫወቱበት። እንደውም ያንደኛውን ምላስ በገመድ ካሰሩ በኋላ ያለምንም ርህራሄ ጎለጎሉት። ከዚያም ሁሉንም ተራ በተራ እግር እና እጃቸውን በመቆራረጥ ገደሏቸው። ይሄን ሁሉ ግፍ የሚፈፅሙት ለ ኢስላምና ሙስሊሞች ካላቸው ጥብቅ ጥላቻ የተነሳ ነው።

ሙስሊሞችም ከኢማሞቻቸው፣ ከኸጢቦቻቸው እና ከዱኣቶቻቸው ለመከላከል እንቅስቃሴ አደረጉ። ቡድሂስቶችም በአፀፋው የሙስሊሞችን መንደር በእሳት አያያዙት። በእሳት አደጋው የተቃጠሉ ቤቶች ቁጥር ወደ 2600 ገደማ ደርሷል። በዚህም ቃጠሎ ምክንያት የሞተው ሞቶ የሸሸውም ሸሸ። ወደ 90,000 የሚደርሱ ሙስሊሞች በየብስም በባህርም ወደ ሌሎች አገሮች ተሰደዱ።

መታረዱም ይሁን መገደሉ አሁንም ድረስ እንደቀጠለ ነው። ሚስቶቻቸው፣ እህቶቻቸው፣ ልጆቻቸው… አይናቸው እያየ የአስገድዶ መደፈር ወንጀል ተፈፅሞባቸዋል።

Wednesday, September 6, 2017

የ10ኛ ክፍል የፈተና ውጤት ማያ

| የ10ኛ ክፍል የፈተና ውጤት ዛሬ ይለቀቃል

Grade 10 Student Information only.

Use Your Registration No. to check your result.


Click here for Grade 12 result.




ከላይ ካልሰራልወት  ከዚሀ ይጫኑ  እናመሰግናለን!!





© 2017 - NEAEA-Ministry Of Education.
Developers

Monday, September 4, 2017

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ






ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ በራያ የቢራ ማስታወቂያ ላይ በትወና መልክ መሳተፌ የሚታወቅ ነው ሆኖም ለተፈጠረው ስህተት ብዙሁን ቅሬታቸውን በኔ ላይ እያሰሙ ነው:: ነገር ግን እኔ በዚህ ማስታወቂያ ላይ በትወና መልክ ከመቅረብ ውጪ ተፈጠሩ የተባሉ ስህተቶች ላይ አለመሳተፌን ለመግለፅ እወዳለው :: አጥፍቼም ከሆነ ይቅርታ ጠይቃለው ::

Source: ሰላም ተስፋየ facebook account