ከጊዜህ ላይ 90 ሴኮንድ ወስደህ ስለ ቡርማ ሙስሊሞችን ችግር ብታውቅ ምን ይመስልሃል?
ታሪኩ ባጭሩ ይህን ይመስላል!

በአንፃሩ ደግሞ ቡድሂስቶች 50,000,000 ይሆናሉ።
ሙስሊሞች የራሳቸውን መንደር በማበጀት የንግድ ልውውጦች እና የራሳቸውን ማህበራዊ ህይወት መምራት ጀመሩ። በዚቹ መንደር ውስጥ የተለያዩ ማህበራት ያሉ ሲሆን መሳጂዶችንና ዱኣቶችን ይደጉማሉ።
አሁንም የቡርማ ቡድሂስቶች ወደ ሙስሊሞች መንደር በመዝመት ከሃገር ለማስወጣት እንቅስቃሴ ጀመሩ። ብዙም ሳይቆይ አሰቃቂ የሆነ ግድያ (እርድ) ፈፀሙ። ይህም የሆነው በሙስሊሞች አካባቢ በመዘዋወር ሰዎችን የሚያስተምሩ ፣ ኒካህ የሚያስሩ ፣ ቁርኣን የሚያስቀሩ ወደ አስር የሚጠጉ ሃፊዞችንና ዳኢዎችን በመያዝ ብርቱ የሆነ ድብደባ ፈፀሙባቸው።
ይህም አልበቃ ብሏቸው ሰውነታቸውን በሳንጃ ተጫወቱበት። እንደውም ያንደኛውን ምላስ በገመድ ካሰሩ በኋላ ያለምንም ርህራሄ ጎለጎሉት። ከዚያም ሁሉንም ተራ በተራ እግር እና እጃቸውን በመቆራረጥ ገደሏቸው። ይሄን ሁሉ ግፍ የሚፈፅሙት ለ ኢስላምና ሙስሊሞች ካላቸው ጥብቅ ጥላቻ የተነሳ ነው።
ሙስሊሞችም ከኢማሞቻቸው፣ ከኸጢቦቻቸው እና ከዱኣቶቻቸው ለመከላከል እንቅስቃሴ አደረጉ። ቡድሂስቶችም በአፀፋው የሙስሊሞችን መንደር በእሳት አያያዙት። በእሳት አደጋው የተቃጠሉ ቤቶች ቁጥር ወደ 2600 ገደማ ደርሷል። በዚህም ቃጠሎ ምክንያት የሞተው ሞቶ የሸሸውም ሸሸ። ወደ 90,000 የሚደርሱ ሙስሊሞች በየብስም በባህርም ወደ ሌሎች አገሮች ተሰደዱ።
መታረዱም ይሁን መገደሉ አሁንም ድረስ እንደቀጠለ ነው። ሚስቶቻቸው፣ እህቶቻቸው፣ ልጆቻቸው… አይናቸው እያየ የአስገድዶ መደፈር ወንጀል ተፈፅሞባቸዋል።
No comments:
Post a Comment