Tuesday, May 16, 2017

የቪዛ መስፈርቶች ለኢትዮጵያ ዜጎች

የቪዛ መስፈርቶች ለኢትዮጵያ ዜጎች በየአገሩ ይለያያሉ። የኢትዮጵያ ዜጎች ወደ ብዙዎቹ አገራት ለመግባት፣ አስቀድሞ ከዚያው አገር ኤምባሲ ወይም ቆንስላ በፓስፖርት ውስጥ የቪዛ (መግቢያ ፈቃድ) ማሕተም ማግኘት አስፈላጊነት ነው። ሆኖም አንዳንድ አገር ያለ ምንም ቪዛ ሂደት ኢትዮጵያውያን ለተወሰነ ጊዜ እንዲጎብኙ ይፈቅዳል፣ እንዲሁም አንዳንድ አገር ኢትዮጵያውያን እዚያ በደረሱበት ጊዜ የመግቢያ ፈቃድ ይሰጣል።



ማስታወሻ - መስፈርቶቹ እንደ መንግሥታት በቶሎ ሊቀየሩ ይቻላል።


ያለ ቪሳ መግባት የፈቀዱ አገራት

  • ኬንያ - ለ3 ወር ያለ ቪሳ መጎብኘት ለኢትዮጵያውያን ይፈቀዳል
  • ሃይቲ - ለ3 ወር " " " "
  • ሴኔጋል - ለ3 ወር " " " "
  • ቤኒን - ለ90 ቀን " " " "
  • ሴይንት ቪንሰንትና ግሬናዲንስ - ለ30 ቀን " " " "
  • ሲንጋፖር - ለ30 ቀን " " " "
  • ማይክሮኔዥያ - ለ30 ቀን " " " "
  • ፊሊፒንስ - ለ30 ቀን " " " "
  • ዶመኒካ - ለ21 ቀን " " " "

ኢትዮጵያውያን በደረሱበት ጊዜ የጉብኝት ቪሳ የሚሰጡ አገራት

እነዚህን አገራት ከመግባት በፊት ቪሳ ማግኘት አስፈላጊ አይደለም። ሌሎች አገራት ሁሉ ግን ከመግባት አስቀድሞ ቪሳ ማግኘት አስፈላጊነት ነው።
  • ኮሞሮስ
  • ካቦ ቨርዴ
  • ጂቡቲ
  • ኡጋንዳ
  • ሞሪታኒያ
  • ርዋንዳ
  • ደቡብ ሱዳን
  • ማዳጋስካር (የ90 ቀን ጉብኝት ቪሳ)
  • ቦሊቪያ (የ90 ቀን " ")
  • ጊኔ-ቢሳው (የ90 ቀን " ")
  • ኒካራጓ (የ90 ቀን " ")
  • ሞሪሸስ (የ60 ቀን " ")
  • ታጂኪስታን (የ45 ቀን " ")
  • ሰይንት ሉሻ 6 ሳምንት " "
  • ሞዛምቢክ (የ30 ቀን " ")
  • ጋና (የ30 ቀን " ")
  • ካምቦዲያ
  • ላዎስ (የ30 ቀን " ")
  • ምሥራቅ ቲሞር (የ30 ቀን " ")
  • ታይላንድ (የ15 ቀን " ")
  • ኢራን (የ15 ቀን " ")
  • ቶጎ (የ7 ቀን " ")
  • ሳሞአ - ለ60 ቀን " " " "
  • ሲሸልስ - ለ3 ወር " " " "
  • ቱቫሉ - ለ1 ወር " " " "
  • ማልዲቭስ - ለ30 ቀን " " " "
  • ፓላው - ለ30 ቀን " " " "

በኢንተርኔት ላይ ቪዛ የሚስጡ አገራት

  • ጂዮርጂያ
  • አንቲጋ እና ባርቡዳ
  • አውስትራሊያ
  • ጋቦን
  • ስሪ ላንካ

የኢትዮጵያ ዜጎች የማይፈቅዱ አገራት

  • ኩዌት

No comments:

Post a Comment